የሀይማኖት ምልክቶችን የሚያንቋሽሹ እና ንፁሀን የሚገድሉ ሰዎች በህግ እንዲጠየቁ ካ?
ጥቅምት 28 2018የሀይማኖት ምልክቶችን የሚያንቋሽሹ እና ንፁሀን የሚገድሉ ሰዎች በህግ እንዲጠየቁ ካልተደረገ ለከፋ ግጭት መንስኤ ሊሆኑ እንደሚችሉ ተነገረ።
በአደባባይ፣ በጎዳናዎች የሚደረጉ ስብከቶችን ጨምሮ የሀይማኖት ዶግማዎችን የሚያንቋሽሹ እና የሚያነውሩ አካላትን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ የሚረዳ ስርዓት ለማበጀት ወይይት ተጀምሯል ተብሏል።
የአዲስ አበባ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ፣ የከተማዋ ኮሚኒኬሽን ጉዳይዎች ቢሮ፣ የሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ከሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን የስራ ሃላፊዎች ጋር በመሆን በሰላም ጉዳይ ላይ በትናንትናው እለት ተወያይተዋል።
አንድ የውይይቱ ተሳታፊ ህጻናትን ጨምሮ ንጹሃን እየተገደሉ ነው፡፡ ይህን ወንጅል የሚፈጽሙ አካላት ለምንድነው በህግ የማይጠየቁት፣ መቼስ ነው የሚቆመው ሲሉ ጠይቀዋል።
ንጹሃን እየተገደሉ እስከመቼ ነው የምንቀጥለው? ሰሞኑን እየተፈጠሩ ያሉ ችግሮችስ መቼ ነው መላ የሚያገኙት? ለምንስ ነው ከምንጩ ማድረቅ ያልተቻለው ሲሉም አከለዋል። አንዱ ሲሞት ሃዘናችን ለምንድነው የጋራ የማይሆነው? ለምንስ ነው መርጠን የምናዝነው? ሲሉ ጠይቀዋል።
መጋቢ አብይ ታደለ የተባሉ ሌላ ተሳታፊ በበኩላቸው የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን አንዱ አላማቸው የራሳቸውን የእምነት ዶግማ ማስተማር እንደሆነ አስታውሰዋል። ሰላም ለማስተማርም ቢሆን ግን ድርሻቸው ከፍተኛ ነው ምክንያቱም ከፍተኛ ተከታይ ስላላቸው ብለዋል።
ነገር ግን በምንሰብክበት ወይም በምናስተምርበት ወቅት የሌላውን ሃይማኖት ልክ አይደልም፡፡ የእኛ ነው ትክክለኛው መንገድ እያልን ነው የምናስተምረው ይህ እንዳያጋጭ የቱ ጋር ነው ሚዛን መጠበቅ ያለብን? ሲሉ ጠይቀዋል።
የከተማዋ ኮሚኒኬሽን ጉዳይዎች ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ዘውዱ ከበደ በከተማዋ በሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን ስም ፍቃድ ወሰደው የሚንቀሳቀሱ በርካታ ሚዲያዎች መኖራቸውን ተናግረው ከእነዚህ ውስጥ ግን የቱ ነው በአግባቡ ስራውን እያሰራ ያለው የሚለውን መለየት አሰፈላጊ ይሆናል ብለዋል።
እነዚህ መገናኛ ብዙሃን እንደ ሃይማኖታቸው አስተምህሮ እየሰሩ ነው ወይ? ተከታዮቻቸውን ማስተማር ችለዋል ወይ? እንዲሁም ወደ አንድነት እና ሰላም ህዝቡን ማምጣት ችለዋል ወይ? ብለን ብንጠይቅ ያለ ምንም ጥርጥር አብዛኞቹ ከዚህ በተቃራኒ የቆሙ ናቸው ሲሉ አስረድተዋል።
የሃይማኖት አስተማሪዎች ስለ ሃይማኖታቸው ሲያስተምሩ አንዱ የሌላውን ልክ አደለም ብሎ ያስተምራል በዚህ እንዴት ነው ሚዛኑን የምንጠብቀው በሚል ከመጋቢ አብይ ለቀረበላቸውጥያቄም አቶ ዘውዱ ሲመልሱ የራስን አስተምህሮ ማስተማር እንጂ ስሌላው አሉታዊ ነገር ማስተላለፍ ተገቢ አይደለም ብለዋል።
የእኔ ልክ ነው የእገሌ ደግሞ ስህተት ብሎ በመገናኛ ብዙሃን ማስተላለፍ ለግጭት ሊዳርግ የሚችል ተግባር መሆኑን ያስረዱት ምክትል ሃላፊው የሃይማኖት አባቶች ማስተማር ያለባቸው አንዱ ከአንዱ የሚለይበትን ነው መሆን ያለበት ብለዋል። የሌላውን መንቀፍ እና ማንቋሸሽ ለግጭት የሚዳርግ መሆኑ መታወቅ አለበት ሲሉም አክለዋል።
የአዲስ አበባ ሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጻሃፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝ በበኩላቸው አንድ ሰው የቱንም ሃይማኖት ቢከተል ሰው በመሆኑ ብቻ ሊከብር እንደሚገባው መታወቅ አለበት ሲሉ ተናግረዋል። መርጦ ማልቀስ አያስፈልግም ያሉት ጽሃፊው ሰው ከተጎዳ ኦርቶዶክስም፣ ሙስሊሙም ሆነ ፕሮቴስታንቱ የኔ ነው በሎ ማሰብ ተገቢ እና ጤነኛ አስተሳሰብ ነው ሲሉ አስረድተዋል።
ለሰው ክብር መስጠት ወሳኝ ነገር ነው ያሉት መጋቢ ታምራት በተለይ ከሃይማኖቶች የሚጠበቀው ለሰው ክብር መስጠት እና ሰላም ነው ብለዋል።
የጎዳና ስብከት እና የጥላቻ ንግግም ቢሆን መላ ሊበጅለት ይገባል የሚሉት መጋቢ ታምራት የአንድን እምነት ቀኖና ማንቋሸሽ፣ ሃይማኖታዊ ምልክትን ማንቋሸሽ አለ እነዚህን ነገር በጊዜ መፍታት ካልቻልን ነገ የግጭት መንስኤ ሊሆኑ ይችላሉ ብለዋል።
የአዲስ አበባ ሰለም እና ጸጥታ ቢሮ በበኩሉ ሰላም ላይ መስራት አለብን ብሏል።
የጋራ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ከሃይማኖት ተቋማት ጋር በጋራ መስራት አለብን እንዲሁም የህግ ማሻሻያ የሚፈልጉ ጉዳዮችንም ተወያይቶ ማስተካከል እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል።
የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ብርሃኑ ረታ የህግ ማሻሻያዎችን ጨምሮ ግብዓት መሆን የሚችሉ ነገሮች መስጠት ደግሞ ከእናንተ ይጠበቃል ሲሉ ተወያዮቹን ጠይቀዋል።
የከተማዋ ኗሪዎች በጎዳናዎች፣ በአደባባዮች እና በንግድ ቦታዎች ሳይቀር እየተጎተትን እንሰበካለን የሚል ቅሬታ በየጊዜው ያቀርባሉ ያሉት ምክትል ሃላፊው ይህን መከልከል የምንችለው በህግ እና በአዋጅ ነው ለዚህ የሚረዳ ሃሳብ ደግሞ ከእናንተ እንፈልጋለን ብለዋል።
በመጨረሻም የሃይማኖት ተቋማት ከሚያራርቁ እና ግጭት ቀስቃሽ ድርጊቶች እራሳቸውን እንዲጠብቁ ጠይቀዋል።
አቶ ብርሃኑ በከተማዋ ከኢትዮጵያዊያን ባህል፣ ወግ እና እምነት የወጡ ለሚዲያ መግለጽ የማይሆኑ ድርጊቶች በርክተዋል፤ ግብረ ገብ ላይ እባካችሁ ስሩ ሲሉ ተማጽነዋል። ትውልዱ ወዴት እየሄደ ነው ሱሊ የጠየቁት ሃላፊው የሃይማኖት ተቋማት እና ሚዲያ ትውልዱ ላይ ካልሰራ እውነተኛ ማንነታችን ይጠፋል ብለዋል።
ያሬድ እንዳሻው ያሰናዳውን በምህረት ስዩም
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s
🐦X : https://x.com/shegerfm?s=2 Receive SMS online on sms24.me
TubeReader video aggregator is a website that collects and organizes online videos from the YouTube source. Video aggregation is done for different purposes, and TubeReader take different approaches to achieve their purpose.
Our try to collect videos of high quality or interest for visitors to view; the collection may be made by editors or may be based on community votes.
Another method is to base the collection on those videos most viewed, either at the aggregator site or at various popular video hosting sites.
TubeReader site exists to allow users to collect their own sets of videos, for personal use as well as for browsing and viewing by others; TubeReader can develop online communities around video sharing.
Our site allow users to create a personalized video playlist, for personal use as well as for browsing and viewing by others.
@YouTubeReaderBot allows you to subscribe to Youtube channels.
By using @YouTubeReaderBot Bot you agree with YouTube Terms of Service.
Use the @YouTubeReaderBot telegram bot to be the first to be notified when new videos are released on your favorite channels.
Look for new videos or channels and share them with your friends.
You can start using our bot from this video, subscribe now to የሀይማኖት ምልክቶችን የሚያንቋሽሹ እና ንፁሀን የሚገድሉ ሰዎች በህግ እንዲጠየቁ ካ?
What is YouTube?
YouTube is a free video sharing website that makes it easy to watch online videos. You can even create and upload your own videos to share with others. Originally created in 2005, YouTube is now one of the most popular sites on the Web, with visitors watching around 6 billion hours of video every month.